Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ እና ሲንጋፖር ትራንስፖርትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመስራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና የሲንጋፖር መንግሥታት በትራንስፖርትና ሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈረማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሲንጋፖር ሪፐብሊክ ኢስታና ቤተመንግስት በነበራቸው ቆይታ÷ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በሁለትዮሽ ምክክር ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም በኢፌዴሪ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሲንጋፖር የትራንስፖርት ሚኒስቴር መካከል የፍላጎት ስምምነት መፈረሙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version