Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከክልሉ መንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር እየተወያዩ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከክልሉ መንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ እየተወያዩ ነው።

ውይይቱ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

በውይይቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አብዱልአዚዝ ዳውድ(ዶ/ር) ÷ከለውጡ በኋላ በክልሉ የተመዘገቡ ውጤቶች ላይ ያተኮረ የውይይት መነሻ ሀሳብ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በዚህም የክልሉ መንግስት የተለያዩ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ሲጎበኙ መቆየታቸው ተመላክቷል፡፡

Exit mobile version