የሀገር ውስጥ ዜና

ከጾታዊ ጥቃት የጸዳች፣ ለሴቶችና ህጻናት የምትመች ሀገር ለመገንባት ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል- ወ/ሮ ያለም ጸጋይ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ወይዘሮ ያለም ጸጋይ ከጾታዊ ጥቃት የጸዳች፣ ለሴቶችና ህጻናት የምትመች ሀገር ለመገንባት ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አሳስበዋል።

የ16ቱ ቀን የፀረ ጾታዊ ጥቃት ንቅናቄ የመዝጊያ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።