Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ አዘርባጃን ገቡ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አዘርባጃን ገብተዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የረጅም ጊዜ ወዳጅና አጋር ሀገር የሆነችው አዘርባጃን መግባታቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀው፤ ለተደረገቸው ደማቅ አቀባበል ለሀገሪቱ መንግስት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በሀገሪቱ በሚኖራቸው ቆይታ በብዙ መስኮች የዘለቀውን ጠንካራ ግንኙነትና ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሻግሩ ምክክሮችና ስምምነቶች እንደሚያደርጉም ገልጸዋል፡፡

Exit mobile version