Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ ቡና ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች መስፍን ታፈሰ እና መሃመድ ኑር ናስር አስቆጥረዋል፡፡

ወላይታ ድቻን ከሽንፈት ያላደነችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ብዙአየሁ ሰይፉ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በሌላ በኩል ሀዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲም ያደረጉት ጨዋታ በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡

Exit mobile version