Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከመላው ኢትዮጵያ የተወጣጡ የባህል ስፖርት ልዑካን የአቃቂ ኢንተርናሽናል ስታዲየምን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከመላው ኢትዮጵያ አካባቢዎች የተወጣጡ የባህል ስፖርት ልዑካን ቡድን አባላት የአቃቂ ኢንተርናሽናል ስታዲየምን ጎብኝተዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላት በአዲስ አበባ በነበራቸው ቆይታ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን እና የወጣቶች ስብዕና ግንባታ ማዕከላትን መጎብኘታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ÷ለዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድር ማስኬጃ እየተሰራ ያለውን የአቃቂ ኢንተርናሽናል ስታዲየምን መጎብኘታቸውን ጠቁመዋል።

Exit mobile version