አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል መንግስትን የ30 ዓመታት ጉዞ የሚያስቃኝ ዓውደ ርዕይ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኦሮሞ ባህል ማዕከል ተከፍቷል።
በሥነ-ሥርዓቱ የክልልና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተዘጋጀው ዓውደ ርዕዩ እስከ መጪው ዓርብ ድረስ እንደሚቆይ ተመላክቷል፡፡
በመራኦል ከድር