Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኦሮሚያ ክልል በለውጡ የተገኙ ውጤቶች ለማስቀጠል ያለመ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ”ለሰላማችን ዘብ እንቆማለን ለውጡን እናጸናለን” በሚል መሪ ሀሳብ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።

በክልሉ ሁሉም ዞኖች ከለውጡ በኋላ የተገኙ ውጤቶች ለማስቀጠል ያለመ ሰላማዊ ሰልፍ መካሄዱም ነው ነው የተገለፀው።

በኦሮሚያ ክልል ከለውጡ በኋላ በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚ መስኮች ከፍተኛ ለውጥ የታየባቸው ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ መግለፃቸው የሚታወስ ነው።

Exit mobile version