የሀገር ውስጥ ዜና

አፈ- ጉባዔዋ በጠሩት የምክር ቤቱ መደበኛ ሰብሰባ ዋዜማ የመልቀቂያ ውሳኔ መስጠታቸው ተገቢነት የለውም- ፌዴሬሽን ምክር ቤት

By Tibebu Kebede

June 08, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አፈ-ጉባኤዋ በጠሩት የምክር ቤቱ መደበኛ ሰብሰባ ዋዜማ የመልቀቂያ ውሳኔ መስጠታቸው ተገቢነት የሌለውና እንደ ብሔር ብሔረሰቦች ተወካይ ኃላፊነት ትክክለኛ ያልሆነ ውሳኔ እንደሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ።

አፈጉባዔዋ ዛሬ ልዩነት አለኝ ብለው በሚዲያ ከመናገራቸው በቀር በእርሳቸው ከሚመራው አስተባባሪ ኮሚቴ ጋር ምንም አይነት ልዩነት እንዳልነበራቸውም ገልጿል።