Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ ጠንካራ ብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት ከገነቡ ሀገራት አንዷ ሆነች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠንካራ ብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት ከገነቡ ስድስት የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

መንግሥት አስፈላጊውን በጀት መድቦ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማትን መገንባት መቻሉ እና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን መሥራቱ ለስኬቱ መገኘት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡

በተጨማሪም መንግሥት ለአሠራር ሥርዓት ዝርጋታ ልዩ ትኩረት መስጠቱ ለውጤቱ መገኘት ከፍተኛ ሚና አበርክቷል ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡

Exit mobile version