አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ማምሻውን ለእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች እና ከተለያዩ ክልሎች ለተወጣጡ አባቶች የኢፍጣር ዝግጅት አድርገዋል።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች እና ከተለያዩ ክልሎች ከተወጣጡ አባቶች ጋር ጠቃሚ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡