Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ምክር ቤቱ ነገ 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ 17ኛ መደበኛ ስብሰባውን እንደሚያካሂድ አስታውቋል፡፡

በስብሰባውም የአንድ የምክር ቤት አባል ያለመከሰስ መብት እንደሚነሳ ይጠበቃል መባሉን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ዘጠኝ ረቂቅ አዋጆችን እንደሚያጸድቅ እና ሁለት ረቂቅ አዋጆችን ደግሞ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች እንደሚመራ ይጠበቃል።

Exit mobile version