Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ያሰለጠናቸው 463 ተማሪዎች አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 463 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላትን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ከተመራቂዎች መካከል 131 የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን አስተምሮ ሲያስምርቅ የዛሬው ለ12ኛ ጊዜ ነውም ተብሏል፡፡

Exit mobile version