አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክ/ከተማ ከ300 በላይ ክፍሎችን የሚይዝ ባለ ዘጠኝ ወለል የመኖሪያ ቤት ግንባታን አስጀምረዋል፡፡
ከንቲባዋ ግንባታውን ባስጀመሩበት ወቅት÷ በአዲስ አበባ ያለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት በትኩረት እየሰራን ነው ብለዋል።
የቤት ግንባታው ለዓድዋ ድል መታሰቢያ ልማት ለተነሱ ዜጎችና በልማት ለሚነሱ ዜጎች መሆኑን ጠቅሰው÷ ግንባታው ሲጠናቀቅም ለከተማዋ የገፅታ ግንባታ ከማላበስ ባለፈ የዜጎችን ህይወትም ያዘምናል ነው ያሉት፡፡
ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ገልጸዋል።