Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች በዳግማዊ አፄ ምኒልክ መታሰቢያ ሐውልት የአበባ ጉንጉን አስቀመጡ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገርን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች በዳግማዊ አፄ ምኒልክ መታሰቢያ ሐውልት የአበባ ጉንጉን አስቀመጡ፡፡

የአበባ ጉንጉኑን ያስቀመጡት÷ የፌደሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና የተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ፣ የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄነራል ዘላለም መንግስቴ እና የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች ዓርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ናቸው፡፡

በተጨማሪም አፈ-ጉባዔ አገኘሁ በቅርቡ በተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በሚገኘው ፓንአፍሪካዊነት ሐውልት ሥር የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡

በአሸናፊ ሽብሩ

Exit mobile version