Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኦሮሚያ ክልል 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር በበጋ መስኖ ስንዴ መልማቱ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በበጋ መስኖ ስንዴ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር በመስኖ ስንዴ መልማቱን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ፡፡

አቶ ሽመልስ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ከ105 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል፡፡

ከከባቢ ሁኔታ ወሳኝነትና ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ የተጀመሩ ሥራዎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡

ጎን ለጎንም ባመረትነው ልክ የመቆጠብ እንቅስቃሴውን አጠንክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

Exit mobile version