Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያና የዓረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት የ49 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና የዓረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት የ49 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
 የድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እና የባንኩ ፕሬዚዳንት ሲዲ ኦልድ ታህ (ዶ/ር) ተፈራርመውታል፡፡
 
ድጋፉ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ምርታማነትን ለማጎልበት የሚውል መሆኑ ተመላክቷል።
 
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት የሚደገፈው ይህ ፕሮጀክት በአራት የተቀናጁ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ እንደሚያተኩር ተገልጿል። 

ድጋፉ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ምርታማነትን ለማጎልበት የሚውል መሆኑ ተመላክቷል።

በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት የሚደገፈው ይህ ፕሮጀክት በአራት የተቀናጁ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ እንደሚያተኩር ተገልጿል።

ስምምነቱ ኦሮሚያን እና ሲዳማ ክልሎችን የሚያካልለውንና 8 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የጊዳቦ ፕሮጀክት አካባቢ የመስኖ መሠረተ ልማት ለመገንባት፣ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ እና ለዘላቂ ዕድገት ወሳኝ የውሃ ሃብት ለማቅረብ ያስችላል ተብሏል።

በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ባንኩ ላደረገው ድጋፍ አድናቆታቸውን መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

 

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version