የሀገር ውስጥ ዜና

የጅቡቲና የኬንያ ፕሬዚዳንቶች በአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ

By Feven Bishaw

February 16, 2024

 

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጅቡቲ ፕሬዚዳንት እስማኤል ኡመር ጊሌ እና የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በ37ኛው የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ አቀባበል አድርገውላቸዋል።