የሀገር ውስጥ ዜና

የቶጎ ጠቅላይ ሚኒስትር አዲስ አበባ ገቡ

By Shambel Mihret

February 15, 2024

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቶጎ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ቶሜጋህ ዶግቤ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል ።

ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱአለም አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።