የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ጥላሁን ከበደ የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ጎበኙ

By Melaku Gedif

February 12, 2024

አዲስ አበባ፣የካቲት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በወላይታ ሶዶ ለሚካሄደው 9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የዝግጅት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም “የዘመኑ ከተሞች ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ ከየካቲት 9 እስከ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ ይካሄዳል፡፡

ለከተሞች ፎረም በወላይታ ሶዶ የሚከናወነው የቅድመ ዝግጅት ሥራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነ መገለጹንም የከተማዋ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡