Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ጥላሁን ከበደ የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣የካቲት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በወላይታ ሶዶ ለሚካሄደው 9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የዝግጅት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም “የዘመኑ ከተሞች ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ ከየካቲት 9 እስከ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ ይካሄዳል፡፡

ለከተሞች ፎረም በወላይታ ሶዶ የሚከናወነው የቅድመ ዝግጅት ሥራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነ መገለጹንም የከተማዋ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version