የሀገር ውስጥ ዜና

መገናኛ ብዙሀን በሀገራዊ ምክክር ሂደት ግንዛቤ መፍጠር ላይ በስፋት እንዲሰሩ ተጠየቀ

By Shambel Mihret

January 29, 2024

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክርን እውን በማድረግ ሂደት መገናኛ ብዙሀን ግንዛቤ መፍጠር ላይ በስፋት እንዲሰሩ ተጠየቀ፡፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ(ፕ/ር) እንደገለጹት÷ መገናኛ ብዙሀን በተለያዩ ቋንቋዎች ለህብረተሰቡ ስለ ምክክሩ ሂደት መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

በርካታ መገናኛ ብዙሀን በምክክሩ የእስካሁን ሂደቶች እና ግንዛቤ መፍጠር ላይ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው÷ ከዚህ በላይ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለገጠሟት ችግሮች በምክክር መፍትሄ ለማበጀት ምክክሩ የሁሉም መገናኛ ብዙሀን አጀንዳ ሊሆን ይገባል ሲሉ ለፋናብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልጸዋል፡፡

በዙፋን ካሳሁን