አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአትክልት ተራ ዋጋን መነሻ በማድረግ የአትክልት እና ፍራፍሬ ዋጋን በመጨመር በሚሸጡ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ቢሮው የኮረና ቫይረስ ከተከሰተ ጀምሮ የንግዱን ማህበረሰብም ሆነ ሸማቹን በፍትሃዊ መንገድ ተጠቃሚ ለማድረግ እና የበሽታውን ተጋላጭነት ለመከላከል በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጿል፡፡