Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት ሕብረተሰቡን በማንቃትና ብርቱ ተሳትፎ በማድረግ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።

ውይይቱ “ለሀገራዊ ምክክር እና ሀገራዊ መግባባት የኪነ-ጥበብ፣ የማስታወቂያ እና የሁነት ዝግጅት ተቋማትና ባለሙያዎች ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ(ፕ/ር ) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት÷ ሀገራዊ ምክክሩ የታለመለት ዓላማ ከግብ እንዲደርስ የሁሉንም ዜጋ እና ተቋማት ርብርብ የሚጠይቅ ነው ።

በተለይም የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ዜጎች በአገራዊ ምክክሩ ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ለማስቻል የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።

ለዚህም የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ሚዲያን በመጠቀም ለሕዝብ ቅርብ የሆኑ ሥራዎችን በመሥራት ለስኬታማነቱ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱም ማሳሰባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Exit mobile version