Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የእስራዔል ጦር ወደ ደቡባዊ ጋዛ እየገፋ መሆኑ ተሠማ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የእስራዔል ምድር ጦር ወደ ደቡባዊ ጋዛ እየገፋ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ወታደራዊ ኃይሉ የሃማስን ማዕከላዊ ዕዞች ፣ የጦር መሣሪያ ማከማቻ ሥፍራዎች እንዲሁም የባሕር ኃይሎቹን ዒላማ አድርጎ እየገፋ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ከሃማስ ጋር የተደረሰው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ሥምምነት ባለፈው አርብ ማብቃቱን ተከትሎ እስራዔል በአዲስ መልክ ጥቃት መክፈቷ ይታወሳል።

በጉዳዩ ላይ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስቲን÷ እስራዔል ራሷን የመከላከል መብት ቢኖራትም ለንፁሐን ደኅንነት መጠንቀቅ እንዳለባት አሳስበዋል፡፡

አስተያየታቸውን ለቢቢሲ የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች ሁኔታው “ከጥፋትም በላይ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስም ÷ እጅግ በጣም በርካታ ፍልስጤማውያን እንደተገደሉ ነው የተናገሩት።

አንድ ሥማቸው ያልተገለጸ የእስራዔል ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ፥ በመሃል ንፁሐን እንዳይጎዱ እስራዔል የምትችለውን ሁሉ እያደረገች ነው ማለታቸውን የዜና ምንጩ አስነብቧል፡፡

በእስራዔል ሃማስ ጦርነት እስካሁን 6 ሺህ ህጻናትን ጨምሮ ከ15 ሺህ 500 በላይ ፍልስጤማውያን ለህልፈት መዳረጋቸውን የጤና ተቋማት ምንጮችን ዋቢ ያደረገው የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version