Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ የጭነት ማጓጓዝ በረራ ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ ወደ ሞሮኮ – ካዛብላንካ አዲስ የጭነት ማጓጓዝ በረራ ለመጀመር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

ወደ ካዛብላንካ የሚያርገው የጭነት በረራ በሰሜን አፍሪካ የመጀመሪያው መሆኑን የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡

ወደ ካዛብላንካ የሚደረገውን የጭነት በረራ ጨምሮም ዓየር መንገዱ በአፍሪካ የሚያደርጋቸው የጭነት በረራዎች ቁጥር ወደ 34 ከፍ ማለቱ ተገልጿል፡፡

Exit mobile version