Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላን በምዕራብ ጃፓን መከስከሱ ተሰማ

190819-N-VE240-1055 PHILIPPINE SEA (Aug 19, 2019) A CV-22 Osprey from the U.S. Air Force 21st Special Operations Squadron in Yokota, Japan conducts flight operations from the flight deck of the aircraft carrier USS Ronald Reagan (CV 76). Ronald Reagan is forward-deployed to the U.S. 7th Fleet area of operations in support of security and stability in the Indo-Pacific region. (Mass Communication Specialist 1st Class Rufus Hucks/Released)

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አንድ የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላን በምዕራብ ጃፓን ያኩሺማ ደሴት ባሕር ዳርቻ መከስከሱ ተሰማ፡፡

ሁኔታውን ተከትሎ የጃፓን የባሕር ጠረፍ ጠባቂዎች ወደ ቦታው የቅኝት መርከቦችን እና አውሮፕላኖችን እንደላኩ ዲፌንስ ብሎግ ዘግቧል፡፡

የጃፓን መከላከያ ሚኒስቴር ምንጮች እንደገለጹት ÷ “ሲቪ-22 ኦስፕሬይ” በመባል የሚታወቀው አውሮፕላን ከመከስከሱ ቀደም ብሎ ጃፓን በሚገኘው የአሜሪካው ዮኮታ የጦር ሰፈር ሥምንት ሰዎችን አሳፍሮ ነበር፡፡

በቀጣናው የአሜሪካ ጦር ኃይሎች ቃል አቀባይ ስለ ተፈጠረው ሁኔታ መረጃ እየሰበሰቡ መሆኑን ተናግረዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version