Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አንጎላ ከኢትዮጵያ ጋር በግብርናው ዘርፍ በትብብር መሥራት እንደምትፈልግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በግብርናው ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መሥራት እንደሚፈልጉ የአንጎላ ፕሬዚዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ ገለጹ፡፡

በአንጎላ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍርቱና ዲበኩ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአንጎላ ፕሬዚዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ አቅርበዋል ።

በዚሁ ወቅትም ኢትዮጵያ በንግድ፣ በግብርና፣ በቱሪዝም እና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ከአንጎላ ሪፐብሊክ ጋር በቅርበት መሥራት እንደምትፈልግ አምባሳደር ፍርቱና ገልፀዋል።

ፕሬዚዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በግብርናው ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበች እንደምትገኝ አንስተዋል፡፡

አንጎላም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መሥራት እንደምትፈልግ መናገራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ዙሪያም÷ ኢትዮጵያ ሥምምነቱን ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር በአፍሪካ ኀብረት ማዕቀፍ ስር ችግሮች እንዲቀረፉ እየሠራች እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version