የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ አሁን ያላት አቅም የቫይረሱን ስርጭት መከላከልና መቆጣጠር ብቻ እንደሆነ ተገንዝቦ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

May 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ አሁን ያላት አቅም የቫይረሱን ስርጭት መከላከልና መቆጣጠር ብቻ እንደሆነ ተገንዝቦ መስራት እንደሚገባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መሪማሪ ቦርድ አሳሰበ።

መሪማሪ ቦርዱ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር አስመልክቶ በሰንዳፋ በኬ ከተማ አስተዳደር የመስክ ምልከታ አድርጓል፡፡