Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከ284 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ284 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዙን የኢፌዴሪ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

224 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር ገቢ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች እና 59 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር ወጪ ዕቃዎች በድምሩ 284 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን በተለያዩ ቅርንጫፎች ተይዘዋል።

ከተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል ተብሏል፡፡

በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ እና የወጪ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር ረገድ ድሬዳዋ፣ አዋሽ እና ሞያሌ ቅርንጫፍ ጽኅፈት ቤቶች ቀዳሚውን ሥፍራ መያዛቸውንም ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version