አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሳዑዲ – አፍሪካ ጉባኤ ጎን ለጎን ከጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ ፣ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሃሰን ሼህ ሞሃመድ ፣ከታንዛኒያዋ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉህ ሃሰን እና ከሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፓል ካጋሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች እንዲሁም ግንኙነቶችን ስለማጠናከር ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ገልጸዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!