አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከሳዑዲ ዓረቢያ ገንዘብ ሚኒስትር መሃመድ አል ጅዳን ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ ልማት እና እዳ ሽግሽግ ላይ መምከራቸውን በሳዑዲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡
የሳዑዲ ዓረቢያ ፋይናንስ ሚኒስትር መሃመድ አል ጅዳን÷መንግስታቸው በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ለሚገኙ የልማት እንቅስቃሴዎች በቀጣይነት ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
ውይይቱ በሪያድ እየተካሄደ ከሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ- አፍሪካ ኢኮኖሚ ኮንፍረንስ ጎን ለጎን ነው የተደረገው፡፡