Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ለአረጋውያን ማዕከል ግንባታ ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች አምባሳደር ሙሐመድ ሳሊም አል ራሺዲ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)÷ ለአረጋውያን የሕክምና፣ የገቢ ማስገኛ እና ሁለገብ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል ማዕከል ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን ለአምባሳደሩ አብራርተዋል፡፡

ደረጃውን የጠበቀ የአረጋውያን ማዕከል ለመገንባት የዲዛይን ስራ ተጠናቅቆ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመው÷ ለግንባታውም የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ድጋፍ እንድታደርግ ጠይቀዋል።

አምባሳደር ሙሐመድ ሳሊም አል ራሺዲ በበኩላቸው÷ የኢትዮጵያ መንግስት በብሔራዊ ደረጃ ለሚያስገነባው የአረጋውያን ማዕከል ሀገራቸው ድጋፍ እንደምታደርግ አረጋግጠዋል።

በኢትዮጵያ አረጋውያንን ጨምሮ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ሕይወት ለመለወጥና ለማሻሻል እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትንም አምባሳደሩ አድንቀዋል።

Exit mobile version