Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ አሕመድ ሺዴ ከሳዑዲ ልማት ፈንድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከሳዑዲ ልማት ፈንድ ዋና ሥራ

አስፈጻሚ ሱልጣን አል-መርሻድ እና ከፈንዱ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሪያድ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ በኢትዮጵያ ውስጥ በሳዑዲ ልማት ፈንድ የሚደገፉ የልማት ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በተመለከተ መክረዋል፡፡

በልማት ፈንዱ በሚደገፉ በኢትዮጵያ እየተገነቡ በሚገኙ ነባር እና ቀጣይ ሊሠሩ በታቀዱ ፕሮጀክቶች ላይም ተወያይተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታደርገው የመሰረተ ልማትና በአጠቃላይ በቀጣናው የሚከናወኑ የልማት እንቅስቃሴዎችን ለመደገፍ ያላቸውን ፍላጎት የፈንዱ ኃላፊዎች አረጋግጠዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version