Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አየር መንገዱ 50 ሜጋ ዋት የሃይል ማስተላለፊያ ሰብስቴሽን አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ 50 ሜጋ ዋት የሃይል ማስተላለፊያ ሰብስቴሽን በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሽፈራው ተሊላ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

የሰብስቴሽኑ ግንባታ ሁለት ዓመት ከግማሽ ጊዜ የወሰደ ሲሆን÷ 9 ሚሊየን ዶላር ወጪ እንደተደረገበት ተጠቁሟል።

ግንባታው በሃይል መቆራረጥ ሳቢያ የሚከሰትን መስተጓጐል እንደሚያስቀርም ተመላክቷል፡፡

በበረከት ተካልኝ

Exit mobile version