አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ገፅታውን በመቀየር ሴት መስሎ በመቅረብ ከአንዲት ግለሰብ ላይ 103 ሺህ ብር አታሎ የወሰደው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡
ቺና በሚል ስም በሴት ፆታ የሚጠራው ግለሰብ በሜካፕ እና በሌሎች ነገሮች ራሱን የሴት ገፅታ አላብሶ ሲንቀሳቀስ እንደነበርና ኳታር እና እንግሊዝ ሃገር እንደኖረ አረብኛ እና እንግሊዘኛም አቀላጥፎ እንደሚናገር የፖሊስ የምርመራ መዝገብ ያመለክታል ፡፡
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።