የሀገር ውስጥ ዜና

ገፅታውን በመቀየር ሴት መስሎ በመቅረብ ከአንዲት ግለሰብ ላይ 103 ሺህ ብር አታሎ የወሰደው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ

By Tibebu Kebede

May 20, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ገፅታውን በመቀየር ሴት መስሎ በመቅረብ ከአንዲት ግለሰብ ላይ 103 ሺህ ብር አታሎ የወሰደው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡

ቺና በሚል ስም በሴት ፆታ የሚጠራው ግለሰብ በሜካፕ እና በሌሎች ነገሮች ራሱን የሴት ገፅታ አላብሶ ሲንቀሳቀስ እንደነበርና ኳታር እና እንግሊዝ ሃገር እንደኖረ አረብኛ እና እንግሊዘኛም አቀላጥፎ እንደሚናገር የፖሊስ የምርመራ መዝገብ ያመለክታል ፡፡

 

#FBC

የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።