የሀገር ውስጥ ዜና

ከሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን በመቅረፍ ግንባታው እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

May 20, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን በመቅረፍ በጥሩ ሁኔታ ግንባታው እየተከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።

58 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ ፕሮጀክት የመስክ ቅኝት ተካሂዶል።