የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ ከ2 ሺህ 700 በላይ በጎዳና ላይ የሚኖሩ አረጋዊያንን የማንሳት ስራ ተጀመረ

By Tibebu Kebede

May 19, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከተለያዩ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከላት ጋር በመተባበር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ 2 ሺህ 754 አረጋዊያንን የማንሳት ስራ ጀመረ።

በዛሬው ዕለትም ከ286 በላይ ኑሯቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ አረጋዊያንን ወደ ክብረ የአረጋዊያን መርጃ ማዕከል የማንሳት ስራ መጀመሩን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ተክሌ ደሬሳ ተናግረዋል።