Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የቤተ-መንግሥት አስተዳደር ከ38 ዓመታት በላይ ላገለገሉ ሠራተኞች እውቅና ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የቤተ-መንግሥት አስተዳደር በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃዎች ከ38 ዓመታት በላይ ላገለገሉ ሠራተኞቹ እውቅና ሰጥቷል።

እውቅና እና የገንዘብ ስጦታ የተበረከተላቸው ሠራኞች እውቀታቸውንና ጉልበታቸውን ሳይቆጥቡና ሳይሰስቱ ሀገራቸውን ለ38 ዓመታት በቅንነት ማገልገላቸው ተገልጿል፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የቤተ-መንግሥት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ዴሬሳ ÷ ሰራተኞች ሀገራቸውን በመውደድ እና በማፍቀር በታማኝነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version