የሀገር ውስጥ ዜና

የኢሬቻ በዓል በየአመቱ እየጎለበተ፣ እያማረበትና እያበበ መጥቶ የሁሉም ኢትዮጵያውያን በአል ሆኖ በማየቴ ታላቅ ደስታ ፈጥሮብኛል – ሽመልስ አብዲሳ

By Tamrat Bishaw

October 06, 2023

ፈጣሪውን በማመስገኑ አብሮነቱንና አንድነቱን በማጠናከር ወደ ስኬት እንደሚመራው ገልጸዋል።

ለውጡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ የባህልና የታሪክ ቦታዎች ግንባታ፣ የባህል ፍርድ ቤቶችን በማቋቋም ፍትህን ለማስመለስ፣ የጠፋ ታሪክን በማረም እና በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ማካተት ላይ ትኩረት በማድረግ ላይ እንገኛለን ብለዋል።

ጀማሮውን በጥብቅ ምርምር በማስቀመጥ በተግባር እናሳያለን ያሉት አቶ ሽመልስ፤ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ሁሉም የኦሮሞ ባህል፣ ታሪክና ቅርስ የአለም የቱሪዝም ማዕከል እንዲሆኑ እየሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በመጨረሻም የኢሬቻ በዓል መሰናክሎችን አልፎ የኦሮሞን ክብር ለአለም አሳይቷል በማለት ገልጸው፤ ለመላው የኦሮሞ ህዝብ፣ ብሄሮችና ብሄረሰቦች መልካም የኢሬቻ በዓል እንዲሆንም ተመኝተዋል።