Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች የውይይት መድረክ አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች “አዲስ እሳቤ በአዲስ ክልል ወደ አዲስ ምዕራፍ ” በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ የውይይት መድረክ አካሂደዋል፡፡

በውይይቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ÷ አዲስ ዕሳቤን በመሰነቅ የክልሉ አመራሮች በመልካም አስተዳደር፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በሌሎች ጉዳዮች ለሕዝብ ምላሽ ለመስጠት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት የሚንቀሳቀሱበት ጊዜ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ከ120 ቀናት እቅዶች ውስጥ በ1 ወር ዕቅድ የተመዘገቡ ውጤቶችና መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮች ላይም ውይይት እንደተደረገ የወላይታ ዞን ኮሙኒኬሽ መረጃ ያመላክታል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version