Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኦሮሚያ ክልል በ80 ሚሊየን ብር ወጪ በጉራጌ ዞን ያስገነባውን ትምህርት ቤት አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል በ80 ሚሊየን ብር ወጪ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ያስገነባውን የጉስባጃይ ኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን አስመርቋል፡፡

ትምህርት ቤቱ 8 ብሎኮች እና 46 ክፍሎች ያሉት ሲሆን በ80 ሚሊየን ብር ወጪ ተገንብቶ ለምረቃ መብቃቱ ተገልጿል፡፡

ለትምህርት ቤቱ ግንባታ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ.ም የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ግንባታው ተጠናቆ ከ250 በላይ ተማሪዎች እየተማሩበት ይገኛል።

በፍቅርተ ከበደ

Exit mobile version