አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በጀርመን የልማትና የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የስደተኞችና ስደተኞች ተቀባይ ሀላፊ ታኒያ ፋብሪሲየስና ልኡካን ቡድናቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በክልሉ በሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች ጉዳይና በሰብአዊና የእርዳታ አቅርቦት ስራዎች ላይ መክረዋል።
በተጨማሪም በሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ ውይይት ማድረጋቸውን ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡