የሀገር ውስጥ ዜና

አስተዳደሩ በመዲናዋ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የውሀ ፓምፖችና ትራክተሮችን አበረከተ

By Feven Bishaw

May 15, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመዲናዋ ለሚገኙ አርሶ አደሮች ከ200 በላይ የውሀ ፓምፖችና 5 ትራክተሮች አበረከተ።

የውሀ ፓምፖቹና ትራክተሮቹን ያበረከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማና የአዲስ አበባ የብልፅግና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ናቸው።