የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ጽ/ቤታቸው ለሚከታተላቸው ፕሮጀክቶች ሰራተኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

By Amele Demsew

September 28, 2023

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጽሕፈት ቤታቸው በሚያሰራቸው እና በሚከታተላቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የመስቀል እና መውሊድ በዓላትን ምክንያት በማድረግ ጽ/ቤታቸው በሚያሠራቸው እና በሚከታተላቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ለሚሰሩ ሠራተኞች በተዘጋጀ የበዓል የምሳ ፕሮግራም ላይ ተገኝተዋል፡፡

በዚህ ወቅትም ለሰራተኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡