Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የመስቀል ደመራ በዓል እሴቱን ጠብቆ እንዲከበር የሕብረተሰቡ ሚና የጎላ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓል ሃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ ሰላም እንዲከበር ሕብረተሰቡ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጥሪ አቀረበ፡፡

ጉባኤው ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ጋር በመሆን የመስቀል የደመራ በዓልን አስመልክቶ ከአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች ጋር ምክክር አካሂዷል።

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ÷ የሃይማኖቱ ተከታዮች በዓሉን ሲያከብሩ አብሮነትን በሚያጎለብት መልኩ ሊሆን ይገባል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Exit mobile version