የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የመሠረተ ልማት ትስስሮች ልዩ ቴክኒካል ኮሚቴን በሊቀ-መንበርነት እንድትመራ ተመረጠች

By Amele Demsew

September 16, 2023

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አህጉራዊና አካባቢያዊ የመሠረተ ልማት ትስስሮች ልዩ ቴክኒካል ኮሚቴን በሊቀ-መንበርነት እንድትመራ ተመርጣለች፡፡

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በታንዛንያ ባካሄው 4ኛው የልዩ ቴክኒካል ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ ኮሚቴውን ለሚቀጥሉት 2 ዓመታት በሊቀ-መንበርነት እንድትመራ በሙሉ ድምጽ ተመርጣለች፡፡

በ4ኛው የልዩ ቴክኒካል ኮሚቴ ስብሰባ ወቅት በህብረቱ ኮሚሽን አማካኝነት የሚከናወነው የአፍሪካ የመሠረተ ልማት ፕሮግራም ለቀጣዮቹ 10 ዓመታት እንዲራዘም መደረጉ ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም÷ ሁሉንም ዓይነት የትራንስፖርት ዘዴዎችን የሚመለከቱ በርካታ መርሐ-ግብሮች መጽደቃቸውን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡