Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ሃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡

አምባሳደር ተሾመ÷ ከአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ተወካይ ም/ ሃላፊ ዴቪድ ክሪቫኔክ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የተመድ ሰብዓዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ራሚዝ አልካባሮቭ እና በኢትዮጵያ የተመድ መልሶ ማቋቋምና ልማት ድርጅት አስተባባሪ ሳልህ ቱራን ጋር ነው የተወያዩት፡፡

በውይይታቸውም ÷ የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን መርሐ ግብርን ለማሳለጥ በትብብር መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

የተቋማቱ ሃላፊዎች በኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፉ መናገራቸውን አምባሳደሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

Exit mobile version