Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ፡፡

በዚሁ መሠረት በክልሉ የጳጉሜ ቀናት የአብሮነት እሴቶችን በሚያሳድጉ፣ የአገልጋይነት ባህልና እሴትን በሚያጎለብቱና ኅብረ ብሔራዊ እሴቶችን በሚያጸኑ የተለያዩ ክንውኖች እንደሚከበር ምክር ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

26ኛው ዓለም አቀፍ የሐረሪዎች ስፖርት እና የባህል ፌስቲቫል በሐረር ከተማ እንዲከበር መወሰኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

ፌስቲቫሉ በተለየዩ ሀገራት የሚኖሩ የክልሉ ተወላጆች እና የሐረሪ ወዳጆች ገንዘባቸውንና እውቀታቸውን ለክልሉ ልማት እንዲያውሉ የሚያስችል መድረክ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም የፌስቲቫሉ በክልሉ መከበር የሐረሪን መልካም ገጽታ ለማስተዋወቅ፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትና የቱሪዝም ክፍለ ኢኮኖሚን ለማጎልበት መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ነው የተባለው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version