አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የ2012 በጀት አመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ዛሬ ገምግሟል፡፡
ባለፋት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የመደበኛ ስራዎች አፈጻጸም ፣ የማሻሻያ ስራዎች ክንውን ፣ የለውጥ ስራዎች አተገባበር እና ሌሎች ተያያዥ ስራዎችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫን ያመላከተ ሪፖርት ቀርቦ በኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች ምክክር ተካሂዶበታል።