የሀገር ውስጥ ዜና

ባለስልጣኑ ባለፉት 9 ወራት የመንገዶች ግንባታ ስራ አፈፃፀም 70 በመቶ ማሳካቱን ገለፀ

By Tibebu Kebede

May 11, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የ2012 በጀት አመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ዛሬ ገምግሟል፡፡

ባለፋት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የመደበኛ ስራዎች አፈጻጸም ፣ የማሻሻያ ስራዎች ክንውን ፣ የለውጥ ስራዎች አተገባበር እና ሌሎች ተያያዥ ስራዎችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫን ያመላከተ ሪፖርት ቀርቦ በኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች ምክክር ተካሂዶበታል።